አማርኛ፣ ኣማርኛ፣ ዐማርኛ ወይስ ዓማርኛ?
-
Upload
befeqadu-z-hailu -
Category
Documents
-
view
365 -
download
5
description
Transcript of አማርኛ፣ ኣማርኛ፣ ዐማርኛ ወይስ ዓማርኛ?
![Page 1: አማርኛ፣ ኣማርኛ፣ ዐማርኛ ወይስ ዓማርኛ?](https://reader036.fdocuments.net/reader036/viewer/2022081719/557206d5497959fc0b8b9c94/html5/thumbnails/1.jpg)
Aማርኛ፣ ኣማርኛ፣ Aማርኛ ወይስ ዓማርኛ?
በበፍቃዱ ኃይሉ
“Eዚህ ግቢ የሚሸጥ Eንጀራ Aለ” የሚል ፅሁፍ Aንድ ግቢ በር ላይ ተፅፎ ባላይ ኖሮ ይህንን ፅሁፍ
ለመፃፍ Aልነሳሳም ነበር፡፡ ማስታወቂያውን Aንብቤ ስጨርስ የሆነ ነገር Eንደጎደለው ተሰምቶኝ ደግሜ
Aስተዋልኩት፡፡ Eርግጥ ነው Eንጀራ የሚለው ቃል ውስጥ ያለችው “E” ለቃሉ ተስማሚ ትክክለኛዋ ሆሄ
Aልነበረችም፡፡ ለቃሉ ሌላ ትርጉም ባትሰጠውም ቅሉ Eኔን ለማደናገር ያክል ግን በቅታለች፡፡
Aማርኛ ቋንቋ የ“ግEዝ” ፊደላትን መጠቀሙ ያጎናፀፈው ፀጋ ለEያንዳንዱ ድምፅ Aንድ ሆሄ ማስቀመጡ
ብቻ Aይደለም፡፡ Aንዳንድ ድምፆች Eንዲያውም ትርፍ ሆሄያት Aሉዋቸው፡፡ Eነዚህ ሆሄያት ከልምድ
ብዛት ከቃላቱ ጋር ይዋሃዱ Eና በAEምሮAችን ይታተማሉ፡፡ ከላይ Eንደገለፅኩት፤ ምናልባት መንትያቸው
ተተክቶባቸው ያነበብናቸው ግዜ ልክ የቃላቱ ትርጉም የተለወጠ ያህል ግር ይለናል፡፡ ይሄ ግን ዛሬ፣ ዛሬ
በብዙ ወጣቶች ላይ የሚስተዋል ነገር Aይደለም፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ወጣቶቹ በAማርኛ Aፃፃፍ ክህሎታቸው
ስለበፀለጉ Aይደለም፡፡ ብዙዎቹ Eንኳንስ ለሆሄያት ግድፈት ሊጨነቁ ይቅርና ዓረፍተ ነገሮቹን ለዛ ባላቸው
መንገድ ገጣጥመው ለመፃፍም Eየተቸገሩ ይገኛሉ፡፡ ለምን?
Eንዳለመታደል ሁኖ ከላይ ላነሳሁት ጥያቄ ፈጣን ምላሽ የሚሰጠኝ የምርምር ፅሁፍ Aጠገቤ Aላገኘሁም፡፡
ይሁን Eንጂ Eኔ በጥያቄው ላይ የራሴን መደዴ መላምት ማስቀመጤ Aልቀረም፡፡ ከነዚህም ውስጥ፡-
ለAማርኛ ትምህርት የተሰጠው ትኩረት Aናሳነት፣
የግEዝ ሆሄያት መብዛት Eና
የፊደሎች ድግግሞሽና የድግግሞሹ ፋይዳ ማጣትን Eንደዓቢይ ምክንያቶች ወስጃቸዋለሁ፡፡
፩ኛ - Aማርኛ ለምኔ?
በAገራችን Aማርኛ ቋንቋ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሥራ ቋንቋ Eንደሆነ በAዋጅ ቢቀመጥም በAፍቃሬ
Eንግሊዘኛ ትውልድ ቅኝ ግዛት ስር መውደቁን ለመረዳት ብዙ ማሰብ Aያስፈልግም፡፡ በጉራማይሌ
ከሚደጎመው ንግግር Eስከተደበላለቀው የታናሽ Eህት ወንድሞቻችን የAማርኛ ፅሁፍ ዋቢ መጥቀስ
Eንችላለን፡፡ ትምህርት ቤቶች ቢያንስ “በEንግሊዘኛ ተነጋገሩ” ማለት ሲቻል “በAማርኛ Aትነጋገሩ” ብለው
የግቢያቸው ማስታወቂያ ሠሌዳዎች ላይ Eስከመለጠፍ ደርሰዋል፣ Eንግሊዘኛ ተናጋሪዎች Eንደሁሉን ቻይ
Eየተቆጠሩ ነው፣ በጥቅሉ ትውልዱ ለAማርኛ የሚሰጠው ዋጋ ወርዷል ብዬ Aምናለሁ፡፡
ለዚህ Eንደዋነኛ መንስኤነት የምኮንነው ለAማርኛ ቋንቋ ትምህርት የተሰጠውን Aናሳ ትኩረት ነው፡፡
ምንም Eንኳን Aማርኛ የብዙዎቻችን Aፍ መፍቻ ቋንቋ ቢሆንም በምርምር (በትምህርት) ብቻ
የሚስተዋሉ የራሱ የሆኑ ሕግጋት Eና Aላባውያን ያሉት መሆኑ Eየታወቀ የመንግስትም ሆነ የግል
ትምህርት ቤቶች ወጣቶች ከቋንቋው ጋር በፍቅር Eንዲወድቁ ትኩረት ሰጥተው Aለመስራታቸው፣
![Page 2: አማርኛ፣ ኣማርኛ፣ ዐማርኛ ወይስ ዓማርኛ?](https://reader036.fdocuments.net/reader036/viewer/2022081719/557206d5497959fc0b8b9c94/html5/thumbnails/2.jpg)
ተማሪዎችን በቋንቋ Aጠቃቀማቸው Eና በፊደል Aጣጣላቸው ጫን ያለ Aስተያየት Aለመስጠታቸው
Aማርኛ ለምኔ ትውልድ ሊያፈራ በቅቷል፡፡
ቋንቋ ሁሉ ሙሉ ነው ከሚለው ኀልዮት በተፃራሪ Aማርኛ ቋንቋ የመግለፅ Aቅም Eንደሚያጥረው
የሚከራከሩ ሰዎችም Eየተበራከቱ ናቸው፡፡ ለዚህ Eንደምክንያት የሚጠቅሱት በከፍተኛ ፍጥነት
Eየበለፀገች ያለችው ዓለማችን በየጊዜው Aዳዲስ ቴክኖሎጂ Aፈራሽ ምርቶችን ታስተዋውቀናለች፡፡ ለነዚህ
ፈጠራዎች ከስያሜ Aንስቶ Aሰራራቸውን ለመግለፅ የሚያስችል Eድገት ግን በቋንቋው ላይ
Aለመስተዋሉን ነው፡፡ ቋንቋውን ከኋላ ቀርነት ጋር ተጣብቆ የቀረ Aድርገው Eንዲያስቡትም
የሚያደርጋቸው ይኸው ነው፡፡ በዚህ ረገድ የሚመለከተው Aካል የሚታይ ስራ የሚሰራ የትርጉም ተቋም
ሊኖረው ይገባል፡፡
ቋንቋን መውደድ ባሕልን ብሎም Aገርን መውደድ ነው፡፡
፪ኛ - ተዘግኖ የማያልቅ የሆሄያት ገበታ
በAማርኛ ቋንቋ ያሉት የሆሄያት ብዛት Aጠያያቂ Aይደለም - ብዙ ናቸው፡፡ ከAማርኛ ይልቅ ለግEዝና
ትግሪኛ የበለጠ የሚያገለግሉትንም ከቆጠርን የፊደል ገበታው ከሦስት መቶ የሚበልጡ ሆሄያትን ይዟል፡፡
ለዚህም ይመስላል ከ‘ሀ’ Eስከ ‘ፐ’ ያሉትን በቅደም ተከተል Aስታውሶ መጥራት ለብዙዎቻችን ፈተና
የሚሆንብን፡፡ ይሁን Eንጂ Aሁንም በየቦታው Eየተስተዋሉ ያሉት ተግዳሮቶች ፊደላቱን የመቁጠር
Aይደለም፡፡ የቋንቋውን ሆሄያት የማምታታት Eና የማሳሳት ፈተናዎች ናቸው፡፡ ከሁሉም Aሳፋሪ
የሚሆነው ደግሞ ግድፈቶቹ Eየታዩ ያሉት ወጣቶችን በሚቀርፁ የሕትመት ስራዎች Eና ሚዲያዎች ላይ
ሳይቀር መሆኑ ነው፡፡
‘ፓ’ን በ‘ፖ’ ማቀያየር የተለመደ ከመሆኑ የተነሳ በተለያዩ ጋዜጦችና በIትዮጵያ ቴሌቭዥንም ጭምር
“ስፖርት” ተብሎ ሊፃፍ የሚገባው “ስፓርት” Eየተባለ ሲፃፍ በተደጋጋሚ ታዝበናል፡፡ ይህ Eንግዲህ
የቋንቋው ሆሄያት በራሳቸው የፈጠሩት ተግዳሮት ነው፡፡ Eነዚህ ፊደላት በማሽን በተለቀመ ፅሁፍ ውስጥ
በቀላሉ የሚለዩ ቢሆኑም በEጅ ጽህፈት ላይ ረቂቅ የስEል ችሎታ Eንዲኖረን Aስገዳጅ ዓይነት ነው፡፡
EንደEውነቱ ከሆነ በተለይ በነዚህ ሁለት ፊደላት (‘ፓ’ Eና ‘ፖ’) Eና መሰሎቹ (‘ጸ’ Eና ‘ደ’፣ ‘ኘ’ Eና
‘ፕ’) መካከል ያለውን ልዩነት ከሰው ሰው በሚለያይ የEጅ ፅሁፍ ውስጥ በAግባቡ Eንዲታይ መጠበቅ
የዋህነት ነው፡፡ Eስከዛሬም ቢሆን ፊደላቶቹን የምንረዳቸው በAገባባቸው ነው፡፡ ይህ ግን በሕትመት
ስራዎች ላይ የሚጠበቅ Aይሆንም - በስነፅሁፍ ስራዎች ላይ ሲከሰት ደግሞ Aሳፋሪ ይሆናል፡፡
Aንዳንድ ጊዜ ግን የማይምታቱትን የማምታታት Aባዜም የሚደጋገሙባቸው Aጋጣሚዎች Aሉ፡፡
Aንዳንዶች በሻ Eና ሾ፣ በባ Eና ቦ፣ በካ Eና ኮ Eና በሌሎችም መካከል ያለውን ልዩነት መረዳት የEድሜ
ልክ ዳገት ይሆንባቸዋል፡፡ የEነዚህን ፊደላት ቅርፅ ለመለየት ምንም ጥበብ Aያስፈልገውም፡፡ መሰረት
የሚጥል የAስተምሕሮ Aካሔድ በመዋEለ ሕፃናት ደረጃ ማስቀመጥ በቂ ይመስለኛል፡፡
![Page 3: አማርኛ፣ ኣማርኛ፣ ዐማርኛ ወይስ ዓማርኛ?](https://reader036.fdocuments.net/reader036/viewer/2022081719/557206d5497959fc0b8b9c94/html5/thumbnails/3.jpg)
፫ኛ - ድምጾች፣ ፊደላቸውና ድግግሞሹ
የAማርኛ የፊደል ሆሄያትን ድግግሞሽ የተመለከቱ ጉዳዮችን ሳነሳ Aንዳንድ የEንግሊዘኛ ተናጋሪዎች
የAናባቢ ፊደላት Aላግባብ መብዛትን በመቃወም የሚያደርጉትን Eንቅስቃሴ Aስታውሳለሁ፡፡ Eነዚህ ሰዎች
Aላግባብ የተደነቀሩ Aናባቢዎች Aስፈላጊ Aይደሉም ጊዜም ይፈጃሉ ስለዚህ ተወግደው ቃላቱ ነፃ መውጣት
Aለባቸው ባይ ናቸው፡፡ ለEንቅስቃሴያቸውም Eንደ መሪ ቃል የሚጠቀሙበት “Enough is enuf!” የሚል
መፈክር ነው - ችግሩን ከነመፍትሄው በAጭሩ የሚያሳይ መፈክር፡፡
የAማርኛ ቋንቋ ፅሁፍ ምንም Eንኳን ከAናባቢዎች ተለጣፊነት የተላቀቀ ቢሆንም የራሱ የሆኑ ድክመቶች
Aብረውት ይኖራሉ፡፡ ቋንቋ ይወለዳል፣ ያድጋል፣ ይሞታልም ከተባለ ሆሄያቱም የቋንቋው Aካላት
Eንደመሆናቸው Aብረው መወለድ፣ ማደግና መሞት ይገባቸዋል፡፡ ይህ ግን በፊደሎቻችን ላይ
Aይስተዋልም፡፡ ለዚህ Eንደምሳሌ የተደረጉ ጥናቶችን ባላገላብጥም ከራሴ ጋር ስጠያየቅ ያስተዋልኩትን
የAማርኛ ፊደል ገበታ Aንድ ችግር ልጥቀስ፡፡ Eንደምናውቀው ሆሄያቱ በድምጽ ላይ (ከግEዝ Eስከ ሳብE
ባሉ ድምጾች) ተመስርተው ነው የተደረደሩት፤ ይሁን Eንጂ Aንዳንድ Aፈንጋጮችም ይገኙበታል፡፡ Eነዚህ
Aፈንጋጭ ሆሄያት የ‘ሀ’ Eና ‘A’ ቤተሰቦች ናቸው፡፡ በ‘ሀ’ Eና ‘ሃ’ ወይም በ‘A’ Eና ‘ኣ’ መካከል ያለውን
የድምጽ ልዩነት መናገር የሚችል ማንም የለም፡፡ ምክንያቱም ሁለቱም የራብE ድምጽ Aላቸው፡፡ ታዲያ
የነዚህ ድምጾች ቤተሰብ የሆኑት የግEዝ ድምጾች የት ገቡ?
መልሱ ቀላል ነው፡፡ ይህንን ክፍተት ለመጣፍ ሲባል ብቻ የተፈጠሩ በሚመስሉ ሌሎች የድምጽ ቤተሰቦች
ውስጥ ተሰድረው Eናገኛቸዋለን፡፡ Eነዚህ ምትኮች ‘ኸ’ Eና ‘ኧ’ ናቸው፡፡ Aባቶቻችን የፊደላቱ መብዛት
ናላቸውን Aዙሮዋቸው ሳያስተውሉ ያለፏቸው ግድፈቶች የሆኑ Eንደሆን Eኛ ‹በቃን!› Eንዳንልና
Eንዳናርማቸው የሚያስገድደን ምንድን ነው፡፡ Eስኪ ከዚህ በታች ‘A’ን ‘ኧ’ ብለን ለማንበብ Eንዲመቸን
ከታች Eናስቀምጠውና የድምጽ ጉርብጣቱ Eንዴት Eንደሚጠፋ Eናስተውል፡፡
ኘ ኙ ኚ ኛ ኜ ኝ ኞ
ኧ U I ኣ ኤ E O
ከ ኩ ኪ ካ ኬ ክ ኮ
ኸ ሁ ሂ ሃ ሄ ህ ሆ
Aባባሌ በ‘A’ ቦታ ‘ኧ’ ወይም በ‘ሀ’ ቦታ ‘ኸ’ ይቀመጥ ሳይሆን ‘ሀ’ Eና ‘A’ በትክክለኛው የግEዝ ድምጻቸው
Eንደ ‘ኸ’ Eና ‘ኧ’ ነው መነበብ ያለባቸው ነው፡፡
ሌላው ጉዳይ ምንም Eንኳን የAማርኛ ሆሄያት የቱንም ያህል የበዙ ቢሆንም ቅሉ ፊደል
ያልተፈጠረላቸው ድምጾች በርካታ መሆናቸው Eሙን ነው፡፡ Eዚህ ሳልጠቅሰው ማለፍ የማልፈልገው
ነገር ግን ላልተውና ጠብቀው ሲነበቡ የተለያየ ትርጉም የሚሰጡ ቃላትን ነው፡፡
የፊደል ገበታችን ብዙ ድምጾችን የተደጋገሙ ሆሄያት ባለቤት Aድርጓቸዋል፡፡ ከነዚህም ውስጥ
‹ሀ፣ሐ፣ኀ›፣ ‹ሠ፣ሰ›፣ ‹A፣A› Eና ‹ጸ፣ፀ› ሳይጠቀሱ Aይታለፉም፡፡ ይሁን Eንጂ ከነዚህ ተመሳሳይ ድምጽ
![Page 4: አማርኛ፣ ኣማርኛ፣ ዐማርኛ ወይስ ዓማርኛ?](https://reader036.fdocuments.net/reader036/viewer/2022081719/557206d5497959fc0b8b9c94/html5/thumbnails/4.jpg)
የሚሰጡ ሆሄያት መካከል Aንዳቸውም ጠብቀውና ላልተው ሲነበቡ የተለያዩ ትርጉም የሚሰጡ ቃላት
መፃፍ የሚቻልበት ሁናቴ Aስቤ ሊመጣልኝ Aልቻለም፡፡ ወይም Aቀያይረን ብንጠቀምባቸው የተለያዩ
ትርጉም የሚሰጡበትን Aጋጣሚ ሕግጋቱ የፈጠሩልን መስሎ Aልተሰማኝም፡፡ ለምሳሌ “መሳሳት” የሚለው
ቃል ሲጠብቅና ሲላላ ሁለት ትርጉም ይሰጣል፡፡ ነገር ግን ይህንኑ ቃል “መሣሣት” ብዬ ብፅፈው ከሁለት
Aንዱን ትርጉም Aይዝልኝም፡፡ ይህ ካልሆነ ድግግሞሻቸው በልምድ ውስጣችን ከታተሙ ቅርፆች የጎላ
ትርጉም የላቸውም፡፡ Eንዲያ ከሆነ ደግሞ የመደጋገማቸው ፋይዳም ለመከራከር የሚያበቃ Aይደለም፡፡
(ከAማርኛ ይልቅ በግEዝ ቋንቋ ውስጥ Aንድ ድምጽን የሚወክሉ ሆሄያት ድግግሞሽ ይበልጥ ትርጉም
Eንዳላቸው ሊቃውንቱ Aበክረው ይናገራሉ፡፡)
በተመሳሳይ ርEስ በከፍተኛ ሁኔታ የሚመሰርቷቸው ቃላት በመጥበቅና በመላላት ሁለት ትርጉም
የሚሰጡባቸው ‘ለ’ Eና ‘ነ’ን የመሳሰሉት የድምጽ ቤተሰቦች ግን Aማራጭ መተኪያ የላቸውም፡፡
Eንደምሳሌ ‹Aለ› Eና ‹ዋና› የሚሉት ቃላት Eንኳን ብንወስድ በቃላቱ ውስጥ ‘ለ’ Eና ‘ና’ Aቻ ሆሄ
ቢኖራቸው ኖሮ ምናልባት የድምጹን መጥበቅ ወይም መላላት Eናመላክትባቸው ነበር፡፡ ስለሆነም የAማርኛ
የሆሄ ገበታ በራሱ የቋንቋውን ሕልውና በማይጎዳ መልኩ ቢሆንም ማነቆ ነው ማለት ይቻላል -
መደገማቸው ፋይዳ የሌለው ድምጾች በተለያየ ቅርፆች ተደጋግመዋል፤ ቢደጋገሙ Eንዲህ Eናደርግባቸው
ነበር የምንላቸው ደግሞ Aቻ የላቸውም፡፡ Eንደኔ፣ Eንደኔ Aባቶቻችን የተዉልንን የፊደል ገበታ
ብንከልሰው ተፅEኖው Eስከምን ድረስ Eንደሆነ ብጠይቅ ድፍረት Aይመስለኝም፡፡ ይህንን ስል ግን ጉዳዩ
ትውልድ የማሰልጠን ያህል ከባድ Eንደሆነ ተስቶኝ Aይደለም፡፡
Eንደማጠቃለያ
ይህንን ፅሁፍ የፃፍኩት በጥንቃቄ Eና በብዙ የሐሳብ ውጣ ውረድ ነው፡፡ ነገር ግን በቀላሉ Aይገኝምና፣
ቀድሞ በተሰራ ጥናት ላይ ተመስርቼ፣ መረጃ Aገላብጬ Eንዳለመሆኑ ድክመቶች ሊገኙበት ይችላል፡፡
EንደAማርኛ ቋንቋ Aፍቃሪነቴ ግን ለAማርኛ Aጠቃቀምና Eድገት ይበጃል ያልኳቸውን ሁሉ መጠቆሜ
ባለሞያዎችን ለጥናት ያነሳሳ ይሆናል ብዬ ገምቼ ነው፡፡ ማንም በፅሁፌ ላይ Aስተያየት መስጠት
የሚፈልግ ሰው በምርምር የተደገፈም ሆነ የግል Aተያዩን Aደባባይ ቢያወጣው ለማድመጥ በጣም
Eጓጓለሁ፡፡
Aማርኛ ቋንቋችን ነው፡፡ ብቸኛው የራሱ ፊደል ያለው የAፍሪካ ቋንቋም ነው፡፡ Eኛ ካልተጠቀምንበት፣
ካላጌጥንበት Eንኳንስ መለያችን ሊሆን ቀስ በቀስ Eንቆቅልሽ መሆኑ Aይቀሬ ነው፡፡ Aማርኛን በወጉ
መማር፣ በAማርኛ መቀኘት ይለምልም፡፡ Aሜን!
![Page 5: አማርኛ፣ ኣማርኛ፣ ዐማርኛ ወይስ ዓማርኛ?](https://reader036.fdocuments.net/reader036/viewer/2022081719/557206d5497959fc0b8b9c94/html5/thumbnails/5.jpg)
ይህንን ጽሁፍ “ፌስቡክ በAማርኛ” የተሰኘ የፌስቡክ ቡድን መወያያ ገጽ ላይ ለጥፌው በነበረበት ጊዜ ብዙ
Aስተያየቶች ደርሰውኝ ነበር፡፡ ሁሉንም Eያመሰገንኩ በወቅቱ ከደረሱኝ Aስተያየቶች መካከል ጥቂቶቹን፣
ለውይይት ይረዳሉ ብዬ በማሰብ Eንደ ጸሃፊዎቹ Aጻጻፍ Eንደሚከተለው Aስፍሬያቸዋለሁ፡፡
ስለሺነህ፡ገላነህ።
ለአቶ፡በፈቃዱ፡ኃይሉ።እጅግ፡በጣም፡ጥሩ፡አያያዝ፡እና፡አስተሣሠብ፡ነው።የድሃ፡መድበልንም፡አንብቤው፡ይበል፡ብያልለሁ።
ግዜ፡እንደ፡ምንም፡አብቃቅቸ፡ደግሞ፡ከዚህ፡በላይ፡ስለ፡ጻፍከው፡ሐሥሣቤን፡ለማክካፈል፡እሞክራልለሁ።በርታ።
Ocean Oc፡- ከነአጻጻፉ መልክቱን ሁሉ ወድጄዋለሁ:: ምስጋና ይግባህ በፈቃዱ::
ሁላችንም በተለይ ደግሞ ወጣቱ ትውልድ ስለ አማርኛ ቋንቋ ያለው እውቀት እና የሚሰጠውን ትኩረት ማንሳትህ በጣም ትልቅ ነገር
ነው::
በትምህርት ቤቶች ጨምሮ በሁሉም ስፍራ እንግሊዝኛ መቀላቀሉ እየተለመደና የስልጣኔም ምልክት እየሆነ መጥቶ ተስፋ የሚያስቆርጥ
ደረጃ ላይ በደረስንበት ጊዜ እንዲህ አይነት እይታ እና ማሳሰቢያ በጣም አስፈላጊ ነው:: ባጠቃላይ ከፊደላቱ አጠቃቀም ጀምሮ በፊት ብዙ
ልብ ያላልኩዋቸውን ነገሮች አይቻለሁ::
ይበል ይበል ብያለሁ::
Dawit Lambebo፡- በጣም ወድጄዋለሁ። ምናልባትስ ድግግሞሹን አጥፍተን አንዱን ሆሄ ብቻ ብንጠቀምስ? ለምሳሌ "ህ" ን ብቻ...
"ፍቅር እስከ መቃብርን" ልብ ይሏል።
ስለሺነህ፡ገላነህ።
ለአቶ፡ዳዊት፡ላምቤቦ፤ የፍቅር፡እስተ፡መቃብር፡ደረሲው፡ክቡር፡ሊቀ፡ምሁር፡ሐዲዲስ፡ዓለማዬሁ፡ልብብ፡እንድንንለው፡
ያደርረጉበትን፡ጠንቅቀን፡ብንናነብበው፤ፊደሎቻችንን፡እንዳልሉ፡ጠብብቀን፡በአጻጻፋችን፡ግን፡የፈልለግነውን፡ፊደል፡ብንን
ጠቀምም፡የኢትዮጵያኛው፡(የዐማርኛው)፡ትርጉሙ፡ስለ፡እማይቀይር፡ለፍጥነት፡እንደ፡እሚምመች፡ነብበረ።ጠብቀው፡ስለ፡
እሚጻፉት፡ፊደሎች፡ደግሞ፡በቤተ፡ክህነት፡ይዘት፡በማለት፡ለዜማ፡አጻጻፍ፡ይጥጠቀሙበት፡የነብበረውን፡ነጥብ፡በፊደሉ፡ራስ
ጌ፡ላይ፡በማመልከት፡አሳይይተውናል፡እንና፡በፊደሎች፡አናት፡ላይ፡ያልሉትን፡ነጥቦች፡በፍቅር፡እስተ፡መቃብር፡ዓይቶ፡ማመሳ
ከር፡ይቻላልል።
ስለሺነህ፡ገላነህ።
ለአቶ፡በፈቃዱ፡ሰላም።መልካም፡ጥረት፡ብቻህን፡በመተ҆ከዝ፡አድርገሃ҆ል።እንደዚህ፡ያ҆ለውን፡አስተሣሠብህን፡ከአነ҆በብከው፡ ፍንጭ፡የመጣ፡አይደ҆ለም፡ለማለት፡ያዳግታ҆ል።ወደ፡ፊት፡ዋቢ፡መጻሕፍትን፡አ҆ገላብጠህ፡ለግዕዝ፡ወይም፡ለኢትዮጵያኛ፡(ዐማርኛ)፡
የ҆ምታቀርበው፡ትችት፡የተገላቢጦሽ፡እንደ፡እ҆ሚሆን፡አል҆ጠራ҆ጠር҆ም።የፊደሎቻችን፡አ ҆መሠራረት፡እ҆ጅግ፡በጣም፡በረቀ҆ቀ፡ምስጢር፡ ነው።ኢትዮጵያውያን፡ፈላስፋዎቹ፡እ҆ነ፡ሄኖክ፡ሐ҆ሣበ፡ባሕርን፡የቆ҆ጠሩ҆በት፣እ҆ነ፡ጥዑመ፡ል҆ሣን፡ያሬድ፡ያዜሙ҆በት፣እ҆ነ፡ዐራት፡ዐይና፡ ጎሹ፡፹፡አሐዱን፡ያስተማሩ҆በት፣………ወዘተ፡እ҆ናም፡ከ”ሀ”፡እስተ፡”ፐ”፡በተራ፡ቁጥር፡የተመዘ҆ገቡ፡ስለ፡ሆኑ፡እ҆ነዚያ፡እዬተቆ҆ጠሩ፡ እ҆ና፡በ፡፲፪፡እ҆ና፡እንደ፡እዬአግባባቸው፡እዬተባ҆ዙ፡እ҆ና፡እዬተገ҆ደፉ፡የዓለማትን፣የከዋክብትን፣ብሎ҆ም፡ትንቢታትን፡በመግለጽ/በመና
ገር፡የኢትዮጵያን፡ሕዝቦች፡እ҆ና፡ክብሯን፡ሲያስጠ҆ብቁ፡የኖሩ҆በት፡ፊደል፡ስለ፡ሆነ፡ምስጢሩ፡ከተከ҆ሰተ҆ልህ፡አንዳች҆ም፡ፊዳል፡ይ҆ቀነስ፡ እንደ҆ማት҆ል፡አምና҆ለሁ። አብዛኛውን፡ግዜ፡ሰ҆ወች፡ሰለ፡ሥልጣኔ፡መዳበር፡ጃፓንን፡ሲያደንቁ፡ይ҆ሰማ҆ል።የቋንቋቸውን፡ሁኔታ፡መርምረህ፡ስ҆ት҆መለከት፡ግን፡ ብዙ፡ች҆ግር፡አ҆ለ҆ባቸው።ያነን፡ች҆ግራቸውን፡ሊያ҆ቃ҆ልሉት፡የቻሉት፣አ҆ናባቢ፡ፊደሎችን፡ከእ҆ናታችን፡ኢትዮጵያ፡ፊደሎቻችንን፡ተበ҆ድ
ረው፡ነው።እ҆ናም፣ለማስረጃ፡ያህል፡ልጥቀስ҆ልህ።አ҆ናባቢዎቹን፡ሂራጋና፡እ҆ና፡ካታካና፡ብለው፡ሠ҆ይመው፣ሂራጋናውን፡ለተወ҆ላጁ፡ ሕዝብ፡ወይም፡ለሀገር፡ውስጥ፤ካታካናውን፡ለውጭ፡ዜጋ፡ወይም፡ለውጭ፡አገር፡ታሪካዊ፡ስም፡ጥበባት፡ይጠ҆ቀሙ҆በታል።ሦስተኛ
![Page 6: አማርኛ፣ ኣማርኛ፣ ዐማርኛ ወይስ ዓማርኛ?](https://reader036.fdocuments.net/reader036/viewer/2022081719/557206d5497959fc0b8b9c94/html5/thumbnails/6.jpg)
ውን፡እ҆ና፡ካንጂ፡ተብሎ፡የእ҆ሚጠራውን፡ቅርፀ፡ምልክት፡ወይም፡ሥዕል፡ደግሞ፡የእ҆ሚ҆ጋ҆ሩት፡ከቻይናወች፡ጋራ፡ነው።አ҆ገላለጼን፡እ ንድ҆ት҆ረ҆ዳ҆ልኝ፡የእ҆ምወደው፡ደግሞ፣ቻይና፡እ҆ና፡ጃፓን፡የራሳቸው፡የሆኑ፡ፊደሎች፡የሌሏቸው፡መሆናቸውን፡እወቅልኝ።ለምሳሌም፦
ዛፍ፡ለማለት፡፩፡የዛፍ፡ሥዕል፡ወይም፡ምሥል፤ጫ҆ካ፡ለማለት፡ከ፪፡በላይ፡የሆኑ፡የዛፍ፡ምሥሎች፡ወይም፡ሥዕሎች፤ተራራ፡ለማለት፡ የተራራ፡ሥዕል፡ውይም፡ምሥል፤…..ወዘተ፡በአ҆ጠቃላይ҆ም፡ምልክቶች፡የእ҆ሚ҆ጠ҆ቀሙ፡ናቸው።እ҆ናም፣ተማሪዎቻቸው፡እነዚህን፡ ምልክቶች፡የማጥናት፡ጭንቀት፡አ҆ለ҆ባቸው።እራሳችውንም፡በስቅላት፡ሕይወታችውን፡በማጥፋት፡የታወቁ፡ናቸው።ለመጠነኛ፡ንባ ብ፡ቢአንስ፡፭፡ሽህምልክቶች፡ማጥናት፡አ҆ለ҆ባቸው።ለምርምር፡ጥናት፡ደግሞ፡ቢያንስ፡፲፡ሽህ፡ምልክቶች፡ማጥናት፡አ҆ለ҆ባቸው። ስለዚህ፡ቅ҆ነሳ፡ብያስፈ҆ልግ፡መ҆ጨነቅ፡ያ҆ለ҆ባቸው፡እ҆ነሱ፡እንጂ፡እኛ፡ፊደሎችን፡ለዓለማት፡አበ҆ዳሪዎች/አዋሾችን፡የእ҆ሚመለ҆ከት፡ አይሆን҆ም።ከዚህ፡በተ҆ረፈ፡በኅዋው፡አውታሩ፡ፈላልገህ፡እንደ፡እ҆ምት҆ጠበብ҆በት፡እገ҆ምታ҆ለሁ።በፊደሎች፡አናት፡ላይ፡እ҆ያመለከ ትኩ፡ለማጥበቂያ፡የተጠ҆ቀምኩባት፡ነጥብ፡ደግሞ፣የእኛ፡ጠ҆በብቶች፡ይዘት፡ብለው፡ሠ҆ይመው፡ለዜማ፡ምንባብ፡ማጥበቂያ፡የተ҆ቀ
ሙ҆ባት፡ኢትዮጵያዊት፡ነጥብ፡ናት።ስለዚህ፡ከላይ፡እንደጠ҆ቀስኩ҆ልህ፦ጃፓኖች፤ሀ ሁ ሂ ሄ ሆ፤ አ ኡ ኢ ኤ ኦ፤ማ ሚ ሙ ሜ ሞ፤ ካ ኩ ኪ ኬ ኮ፤ ና ኑ ኒ ኔ ኖ፤ ያ ዩ ዬ ዮ፤ሳ ሱ ሲ ሴ ሶ፤ ታ ቱ ቴ ቶ፤ ዳ ዱ ዴ ዶ፤ራ ሩ ሪ ሬ ሮ፤…….ወዘተ፡በ፡
ማለት፡ በእ҆ሚጽፏቸው፡ምልክቶች፡ ጐን፡ካልጻፏቸው፡በስተቀር፡ ማ҆ንም፡ጃፓናዊ፡አንብቦ፡መረዳት፡አይችል҆ም። እንደዚያ፡አድርገው፡ካልጻፉ፡አንባቢው፡ደውሎ፡ምን፡ዓይነት፡ምልክት፡እንደ፡ተጻፈ፡ነግሮ፡ጸሐፊው፡ያስረ҆ዳዋ҆ል።ለወፊቱ፡ ተመራማሪዎቻችን፡ከጻፏቸው፡መጻሕፍት፡፩፡ወይም፡፪፡ሳ҆ታነ҆ብ፡መጻፉ፡/አስተያዬት፡መስጠቱ፡ለወ҆ጣቱ፡ትውል҆ድ፡ግራ፡የ፡ እ҆ሚያ҆ጋ҆ባ፤ለኢትዮጵያ፡እ҆ና፡ሕዝቧ፡በ҆ጣ҆ም፡አደገኛ፡ስለ፡ሆነ፡- ቢያንስ፡ኢትዮጵያ፦ የዓለሙ፡መ҆ፋረጃን፡በክቡር፡ንቡረ፡ዕድ፡ ኤርምያስ፡ከ҆በደ፡ወልደ፡ኢየሱስ፡ከተጻፈው፡ጀ�ምር።ለማናቸውም፡የ፡እሚከተሉትን፡ምንባብ፡ጋብዠሃለሁ፦ ፩ኛ- www.ekogs.org ፪ኛ-http://www.assimba.org/Articles/YeEthiopia_Kalendar_Tarik.pdf በተረፈ፡ደህና፡እንሁን።
የኔ መልስ፡- ውድ ስለሺነህ ገላነህ፣
ለመልስ ምት ጽሁፍህ እና ምክርህ እጅግ አድርጌ አመሰግንሃለሁ፡፡ የጽሁፍህ ይዘትና መደምደሚያ ለእኔ እንደገባኝ በጥናት ላይ
ያልተመሰረተ ጽሁፍ መፃፌ ትውልድ የሚያጠፋ ስህተት መሆኑን ልትነግረኝ ፈልገሃል፡፡
ይሁን እንጂ የጽሁፌን መንፈስ አጣጥመህ የተረዳህ አልመሰለኝም፡፡ ምክንያቱም በጽሁፉ ውስጥ አማርኛ ቋንቋ እንደማንኛውም ቋነቋ
ሙሉ መሆኑ ተገልፆ፤ ፊደላቱም የአፍሪካ ብቸኛ ኩራት መሆናቸው ተነግሯል፡፡ ይሁን እንጂ የአማርኛ ጽሁፍ የሚወለጋገድባቸው
ወጣቶች መብዛታቸው የአደባባይ ምስጢር ነውና ምን ይሆን መንስኤው ለሚለው መልስ ለመስጠት እንደ ‹አማርኛ አፍቃሪነቴ›
የተውተረተርኩበት ጽሁፍ ነው፡፡ በመሰረቱ በቅኝት (observation) ላይ የተመሰረተ ጥናታዊ ጽሁፍ ማድረግ አይቻልም ያለው ማነው?
በጽሁፉ ላይ ለመንስኤዎቹ ‹መደዴ› ብዬ የጠቀስኳቸውን መላ ምቶች ያስቀመጥኩ ቢሆንም ‹መደዴ› የሚለው ቃል እንደው ለትህትና
ይሁነኝ ብዬ ያደረግኩት እንጂ ለነገሩስ በጣም ለረዥም ጊዜ ሳሰላስል እና መላምቴን ስህተት የሚያደርጉ እውነታዎች ያሉ እንደሁ
ሳፈላልግ ቆይቼ ነበር፡፡ ለምሳሌ በፊደል ገበታችን ላይ የ‹ሀ› እና ‹አ› ግዕዝ እና ራብዕ ድምፆች ተመሳሳይነት በፊደሉ ፈጣሪ አባቶቻችን
ስህተት እንዳልተፈጠረ የሚነግረኝ ተመራማሪ እንደማይመጣ በሙሉ ልብ እወራረዳለሁ፡፡
እኔ በአማርኛ ጽሁፍ እና አጻጻፍ ዘይቤ በፍቅር ወድቄያለሁ፡፡ ቋንቋ ይወለዳል፣ ያድጋል፣ ይሞታልም እንዲሉ አማርኛም በዘመኑ ብዙ
ጥቃቅንና ግዙፍ ለውጦችን እያስተናገደ እዚህ መድረሱ አይካድም፡፡ በጉልህ ብንመለከተው እንኳን የአባቶቻችን አባቶች አማርኛን
ፈጥረውታል፣ አባቶቻችን ፊደል ሰጥተውታል፣ እኛ ደግሞ ፊደላቱ ላይ የምናገኛቸው ግድፈቶችን አርመን ለልጆቻችን ብናስተላልፈው
ምንድን ነው ችግሩ? ዓለም ጎዶሎ እንደመሆኗ ሁሉም ስራዎች ሙሉ ሊሆኑ አይችሉም፡፡ እንደመታደል ሁኖ ግን ዓለም ለውጥ ላይ ናት፡፡
ለውጥ አማጪዎችም እኛ በመሆናችን ዓለማችንን ስትለወጥ ማየት እንችላለን፡፡ ለምሳሌ አማርኛችን ላይ ያሉትን ድክመቶች በማረም፡፡
በነገራችን ላይ ክቡር ዶ/ር ሐዲስ አለማየሁ የሚጠብቁ ፊደላት አናት ላይ ዘማሪ ዳዊት ከተጠቀመባቸው 10 የዜማ ምልክቶች መካከል
ይዘት የተሰኘውን ትዕምርት በማስቀመጥ እንዲለዩ በድንቅ ስራቸው ‹ፍቅር እስከ መቃብር› የጠቆሙትም በኔው ዓይነት አጻጻፉ ላይ
![Page 7: አማርኛ፣ ኣማርኛ፣ ዐማርኛ ወይስ ዓማርኛ?](https://reader036.fdocuments.net/reader036/viewer/2022081719/557206d5497959fc0b8b9c94/html5/thumbnails/7.jpg)
እንዲሻሻሉ የሚጓጉላቸውን ስርዓቶችን እያመለከቱ መሆኑን ልብ ይሏል፡፡
በተረፈ ተቆርቋሪነትን ከልብ አደንቃለሁ፡፡ እኔም አንተም የምንጮኸው ለአንድ አላማ - ለአማርኛ ትንሣኤ ብሎም ልዕልና ነውና፡፡
ስለሺነህ፡ገላነህ፣በስለሺነህ።
በፈቃዱ፦ የጽሁፍህ ይዘትና መደምደሚያ ለእኔ እንደገባኝ በጥናት ላይ ያልተመሰረተ ጽሁፍ መፃፌ ትውልድ የሚያጠፋ ስህተት መሆኑን
ልትነግረኝ ፈልገሃል፡፡
ስለሺነህ፦ አዎ!።እንደዚህ፡ግራ፡የተጋባው፡ትውልድ፡ነው፡እያልክ፡በአወንታ፡ልቀበልህ፡መከጀልህ፡ገረመኝ።
በፈቃዱ፦ ይሁን እንጂ የጽሁፌን መንፈስ አጣጥመህ የተረዳህ አልመሰለኝም፡፡............. ይሁን እንጂ የአማርኛ ጽሁፍ የሚወለጋገድባቸው
ወጣቶች መብዛታቸው የአደባባይ ምስጢር ነውና ምን ይሆን መንስኤው ለሚለው መልስ ለመስጠት እንደ ‹አማርኛ አፍቃሪነቴ›
የተውተረተርኩበት ጽሁፍ ነው፡፡
ስለሺነህ፦ አቀራረብህ፡በማር፡ላይ፡የተለወሰ፡እሬት፡እንደ፡ሆነ፡ተገንዝቤዋለሁ።እርግጠኛ፡ለወጣቱ፡የምታስብ፡ቢሆን፡ኖሮ፡
ጥያቄህ፡ከፊደሎቻችን፡መወለድ፣ማደግ፣እና፡መሞት፡ላይ፡ትኩረት፡ሰጥተህ፡የሞት፡ፍርድ፡ውስጥ፡አትገባም፡ነበር።ለምን፡በአ
ማርኛ፡መሠረተ፡ትምህርት፡ስለ፡ሌላቸው፡እንደ፡ሆነ፡ሳይታወስህ፡ቀርረ?።አብዛኞቹ፡በሊሴ፡ገብረ፡ማርያም፣ቅዱስ፡ዮሴፍ፣...
ወዘተ፡ገብተው፡የተማሩት፡ናቸው።አስተሳሰባቸውንም፡ማስተካከል፡ያቃታቸው፡በውጭ፡ሰወች፡ስለ፡ተማሩ፡እና፣የውጭ፡ዜጎች፡
ደግሞ፡ባሕላቸውን፡ለማስተዋወቅ፡የሚጥሩ፡መሆናቸውን፡እንዴት፡አላሰብክም።
በፈቃዱ፦ መላምቴን ስህተት የሚያደርጉ እውነታዎች ያሉ እንደሁ ሳፈላልግ ቆይቼ ነበር፡፡ ለምሳሌ በፊደል ገበታችን ላይ የ‹ሀ› እና ‹አ›
ግዕዝ እና ራብዕ ድምፆች ተመሳሳይነት በፊደሉ ፈጣሪ አባቶቻችን ስህተት እንዳልተፈጠረ የሚነግረኝ ተመራማሪ እንደማይመጣ በሙሉ
ልብ እወራረዳለሁ፡፡
ስለሺነህ፦ ለመሆኑ፡ዐዋቂዎች፡ምሁራንን፡ጠቀህ፡አናውቅም፡ብለውሃል፡ወይ?።ስለ፡ፊደሎች፡ልዩነት፡በሚብባ፡ልዩነት፡ስለ፡
ረጋ፡ብለህ፡አተነፋፈስህን፡እና፡በጉሮሮህ፡አጠቃቀም፡ተለማመድ።እራሳቸውን፡ከፍከፍ፡የሚያርጉ፡ይዋርውዳልሉ፡የተባለውን፡
አስስብ።
በፈቃዱ፦ በነገራችን ላይ ክቡር ዶ/ር ሐዲስ አለማየሁ የሚጠብቁ ፊደላት አናት ላይ ዘማሪ ዳዊት ከተጠቀመባቸው 10 የዜማ ምልክቶች
መካከል ይዘት የተሰኘውን ትዕምርት በማስቀመጥ እንዲለዩ በድንቅ ስራቸው ‹ፍቅር እስከ መቃብር› የጠቆሙትም በኔው ዓይነት አጻጻፉ
ላይ እንዲሻሻሉ የሚጓጉላቸውን ስርዓቶችን እያመለከቱ መሆኑን ልብ ይሏል፡፡
ስለሺነህ፦ ታዲያ፡እንደዚህ፡መሆኑን፡ካወቅህ፣እንዴት፡የአማርኛችንን፡ሥርዓተ፡ጽሑፍ፡ባልተከተለ፡አጻጻፍ፡ትጽፋልለህ?።ስለ፡
ክቡር፡ሐዲስ፡ዓለማዬሁ፡መተቸት፡ደግሞ፡የምታውቅ፡አልመስሰለኝም።ፊደሎቻችንን፡በተመለከተ፡በጻፉት፡ሊቀ፡ምሁራን፡አዝ
ነው፡ተችተውበት፡"ልብ፡ወልለድ"፡ስለ፡ሆነ፡ይቅርታ፡አድርገውልላቸዋል።የአጻጻፋቸው፡ባሕላችንንም፡የሚያስተዋውቅ፡በመ
ሆኑ፡ጭምምር።ለአንባቢዎቼ፡እታወዋልለሁ፡ብለው፡ስለ፡ነብበረ፡በግትርነት፡አልቆሙም።ቸር፡ነገር፡ያምጣልልን።ደህናም፡
እንሁን።
የኔ መልስ፡- ውድ አቶ ስለሺነህ ገላነህ፡
ስለስህተት አስቀያሚው ነገር እየሰራነው አይታወቀንም፡፡ አሁን የኔና ያንተ ምልልስ ኃይለ ቃል አዘል ዓ/ነገሮችን መያዙ የታመነ ነው፡፡
ግባችን ስለአማርኛ ቋንቋ ዕድገት መወያየት እና አዳዲስ ነገሮችን መጠቆም ሳይሆን እኔ ነኝ ካንተ የተሻለ ለወጣቱ አሳቢ፣ እኔ ነኝ ካንተ
የተሻለ ለአማርኛ ተቆርቋሪ እያሉ መፎካከር መሰለ፡፡ ይሁን እሰዬው ምክንያቱም ሁለታችንም እሰጥ-አገባ ውስጥ የገባነው ለአገራችን
ዜጎችና ቋንቋ ሕልውና ጥብቅና በመቆም ነው፡፡
ለአስተያየትህ ምላሽ ሳስቀምጥ ‹ዘማሪ ዳዊት› የሚል ቃል ተጠቅሜ ነበር፣ አንተም ይህንኑ ሳታስተውል ደግመኸዋል፡፡ ነገር ግን ‹ዘማሪ
ያሬድ› ነበር ትክክለኛው ስም፡፡ አየህ ስትሳሳት አይታወቅህም፤ ቢታወቅህማ ለምን ትሳሳታለህ - ብትሳሳትም ቀድመህ ታርመዋለህ፡፡
ሐዲስ አለማየሁ ተወቅሰው ይቅርታ ጠይቀዋል ብለሃል፡፡ ያ ማለት ግን ሐዲስ አለማየሁ ይቅርታ የሚያስጠይቅ በደል ሰርተዋል ማለት
አይደለም፡፡ እኔ ስለሳቸው የተናገርኩትም የሚለው ይህንኑ ነው፡፡ እርሳቸው እንዲህ ቢሻሻል ጥሩ ነው የሚል ተስፈኛ ጥቆማ አበረከቱ
![Page 8: አማርኛ፣ ኣማርኛ፣ ዐማርኛ ወይስ ዓማርኛ?](https://reader036.fdocuments.net/reader036/viewer/2022081719/557206d5497959fc0b8b9c94/html5/thumbnails/8.jpg)
እንጂ አማርኛ ከዚህ የተሻለ አማራጭ የለውም የሚል መደምደሚያ አላስቀመጡም፡፡
ስለሊሴ ተማሪዎች እና ሌሎችም የተናገርከውን ግን እኔ አልቀበለውም፡፡ ምንም እንኳን አንዳንድ የግል ትምህርት ቤቶች በአማርኛ
ትምህርት ደካማ አቋም እንዳላቸው በዋናው ጽሁፌ በግልጽ ያስቀመጥኩት ቢሆንም ቅሉ ሌሎች ብዙ የግል ትምህርት ቤቶች ከመንግስት
ት/ቤቶች የተሻለ የአማርኛ ትምህርት ይሰጣሉ፡፡ የጠቀስኩት ችግር በይበልጥ የሚስተዋለው እንዲያውም በመንግስት ትምህርት ቤት
ተማሪዎች ናቸው፡፡ በዚህ ዘመን እየተስፋፋ በመምጣት ላይ ካለው የዘመናዊ ትምህርት አኳያ ሁሉንም ሰዎች የቄስ ትምህርት ቤት መላክ
እንዳለብን ማሰብ ደግሞ ዘመኑን ከግንዛቤ ያላስገባ የዋህነት ነው፡፡
ስለትህትና ያወራኸውም ከፊል እውነታ አለው፡፡ ይሁን እንጂ ገና ለገና መታበይ ይሆንብኛል ብዬ እኔ የተናገርኩት ስህተት ነው ብዬ
ያለስህተቴ ራሴን ላዋርድ አልፈቅድም፡፡ ስለፊደላቱ (አ እና ሀ) ግዕዝና ራብዕ ድምጾች አንድነት በስህተት መፈጠር ዛሬም ቅንጣት
ጥርጣሬ እንደማይገባኝ ደግሜ እናገራለሁ፡፡
ለማንኛውም ስለስህተት ያወራሁት እንዲሁ አይደለም፡፡ በዋናው ጽሁፌ ውስጥ የሰፈረ (አንተ እንዳልከው ወጣቱን የሚያጠፋ፣ ቋንቋውን
የሚገድል) ስህተት ካለ እባክህን ይሄ፣ ይሄ በለኝ፡፡ ይቅርታ አልጠይቅህም - ግን የጽሁፌ አላማ ግቡን ይመታል፡፡ በጽሁፉ እንዳሰፈርኩት
ስለአነሳሁዋቸው ችግሮች አንድም አማራጭ ምላሽ/መፍትሄ አገኛለሁ አሊያም ችግሮች ያልኳቸው ችግሮች አለመሆናቸውን እረዳለሁና!